Showing posts with label ምግባረ ሠናይ. Show all posts
Showing posts with label ምግባረ ሠናይ. Show all posts

Saturday, September 22, 2018

መንፈሳዊ ዜና


   ሰላም ጤና ይስጥልኝ ይህ የሃይማኖት እውቀት ማስፋፊያ ማህበር መንፈሳዊ ዜና ነው ዜናውን የሚቀርብላችሁ የማህበር ጽ/ቤት ነው

ቤዛ ብዙሃን ምግባረ ሰናይ ማህበር ለሚያስተምራቸው ለ150 ተማሪዎች ለ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መማሪያ የሚሆን የትምህርት መገልገያ ቁሳቁሶችን አከፋፈለ

   ዝርዝሩም  ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናል
ቤዛ ብዙሃን ምግባረ ሰናይ ማህበር በማህበራዊ እሴቶች ላይ በርካታ ስራ እየሰራ ያለ ሲሆን ለ45 አረጋዊያን በያሉበት ቦታ ወርሀዊ በጀት መድቦ እየጦረ ይገኛል አሁንም የ2011 ዓ.ም የትምህርት ዘመንን ምክንያት በማድረግ ለሚያስተምራቸው 150 የቀለም ተማሪዎች ቦርሳ ፤ ደብተር ፤ እስክሪብቶ ፤ እርሳስ ፤ መቅረጫ  እና ማስመሪያ በሚያስፈልጋቸው የትምህርት ደረጃ መሰረት አከፋፍሏል


            

የሃይማኖት እውቀት ማስፋፊያ ማህበር/የዕማማ የ34ተኛ ዓመት የወንጌል አገልግሎት የምስረታ በዓሉን ሊቃነ ጳጳስና የተለያዩ አድባራት አና ገዳማት  አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በሰገነት ባህታዊት ኪዳነ ምህረት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በደመቀ ሁኔታ አከበረ እግዚአንሔር ይመስገን

    ዝርዝሩም  ከዚህ እንደሚከተለው ይሆናል
በዓሉን ያስጀመሩት የሃይማኖት እውቀት ማስፋፊያ ማህበር መስራች እና የበላይ ጠባቂ የሆኑት ሊቀ ተጉ.መ/ር ገ/መስቀል ኃ/መስቀል በ1ኛ ዩሀንስ መልዕክት ም 1 ቁ 5 ላይ ያለውን ሀይለ ቃል እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም በሚለው ሀይለ ቃል በመጠቀም ያለፉትን የጥንካሬ ተምሳሌት የሆኑትን ስራዎች አስታውሰው እንኳን ለ34ተኛ ዓመት በብርሀን ለሚመላለሰው የወንጌል አገልግሎት ጉባኤአችን በሰላም አደረሳችሁ የሚል መልእክት ካስተላለፉ በኋላ በቀጥታ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ኤጲፋኒዎስ መድረኩን አስረክነዋል፡፡

Saturday, September 15, 2018

ለችግረኛ ልጆች የትምህርት ቤት ማቴርያል አድለናል

ዛሬ መስከረም 5 ቀን 2011 ዓ.ም በሃይማኖት እውቀት ማስፋፊያ ማህበር ሥር የተቁዋቁዋመው የቤዛ ብዙኃን ምግባረ ሠናይ በጎ አድራጎት ማህበር በማህበሩ መሥራች በሊቀ ትጉ / /መስቀል /መስቀል አስተባባሪነት ለሚጀመረው የትምህርት ዘመን ለችግረኛ ልጆች የትምህርት ቤት ማቴርያል ቦርሳ ደብተር እስክሪብቶ እርሳስ ወዘተ በማህበሩ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ 120 መቶ ሃያ ልጆች በዚህ መልኩ አድለናል እግዚአብሔር ይመስገን 






Saturday, September 01, 2018

በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ለደረሰው ችግር እርዳታ ተደረገ


በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ለተቃጠሉትና ጉዳት ለደረሰባቸው አብያተ ክርስትያናት ማቁዎቁሚያ እና ለተፈናቀሉ ሰዋች እርዳታ ለማድረስ የሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ ማህበር መስራች አና የበላይ ጠባቂ የሆኑት ሊቀ.ትጉ.. /መስቀል /መስቀል 400 ኩንታል ሚጉዋጉዋዝበት 35,000 (ሰላሳ አምስት ) ብር ለኮሚቴው ሰብሳቢ አስረክበዋል ለወደፊትም ለተባባሪዋቻችን ለዚህ ጉዳይ መርዳት ለምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000254922898 መላክ የምትችሉ መሆኑን ኮሚቴዉ ያሳስባል ስለ ትብብራችሁ ከልብ አመሰግናለሁ፠


Saturday, July 14, 2018

የነዳያን ምሳ ግብዣ ተከናወነ


ዛሬ ሀምሌ 7 ቀን 2010 ዓ.ም የአብርሃሙ ስላሴን ዓመታዊ ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ በሊቀ ትጉሃን መምህር ገብረ መስቀል የሚመራው ማህበር በምዕራፈ ቅዱሳን የሰገነት በሕታዊት ኪዳነ ምህረት ቤተ ጸሎት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የነዳያን ምሳ ግብዣ አከናወነ 


ከፎቶ ማህደር






Friday, April 27, 2018

የነዳያን የምሳ ግብዣ ተከናወነ


መንፈሳዊ ዜና እናቀርባለን ውድ ወገኖቻችን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትሳኤውን ምክንያት በማድረግ ሚያዚያ 1 ቀን 2010 . በርካታ ቁጥር ያላቸውን ነዳያን በመጋበዝ በማህበሩ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የምሳ ግብዣ ተደርጎአል እግዚአብሔር ይመስገን በጉልበት በማቴሪያል በገንዘብ ለረዳችሁን ሁሉ በነዳያኑ ስም ከልብ እናመሰግናለን የበአል ዝግጅት ኮሚቴው።